Saturday, November 30, 2013

ከኢትዮጵያ ዜጎች ጋር በተያያዘ በሳውድ አረቢያ ከፍተኛ የሆነ አደጋ ማንዣበቡን ኢትዮጵያውያን ተናገሩ



ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ የሚታየው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው ዜጎች። ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያን በእስር ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቀናቸውን ይጠባባቃሉ። የኢትዮጵያ መንግስት በመቶ ሺ የሚቆጠረውን ስደተኛ ለማስተናገድ የመደበው የሰው ሀይል 40 ብቻ ነው። የሳውድ አረቢያ መንግስት ደግሞ በተዘዋዋሪ መንገድ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ ምድር ተጠራርገው እንዲወጡ እየቀሰቀሰ ነው። ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ አደጋ ሊፈጠር ይችላል ብሏል  አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ ጋዜጠኛ።
በዛሬው እለት በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተነው የኤስ ኤም ኤስ መልዕክት  ህጋዊ ለተባሉትም ሆነ ህገወጥ ለሚባሉት ኢትዮጵያውያን የማስጠንቀቂያ ደወል ነው ይላሉ እኝህ ጋዜጠኛ።



በሞባይል ስልኮች የተበተነው ኤስ ኤም ኤስ ኢትዮጵያውያንን ቀጥራችሁ የምታሰሩ እንዲሁም መኖሪያ ቤት ያከራያችሁ ሁሉ በአስቸኳይ እንድታስወጡ፣ ይህን ባታደርጉ ግን 100 ሺ ረያል ትከፍላለችሁ የሚል እንደሆነ ያነጋገርናቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል። ይህን መልእክት ተከትሎ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከተከራዩበት ቤት ተባረዋል። 9 ኢትዮጵያውያንን ወደ አስጠጋው ኢትዮጵያዊ በመደወል መታሰቢያ ቀጸላ አነጋግራቸዋለች። እርሱ እንደሚለው መልክቱ መተላለፉን ተከትሎ ጓደኞቹ ከቤታቸው እንዲወጡ ተደርጎ በእርሱ ቤት ተጠልለዋል::
ከቤታቸው ከተባረሩት መካከል አንዱ ከ8 ወራት በፊት አባቱ ቤታቸውን ሸጠው ፣ በኪራይ ቤት እየኖሩ በህጋዊ መንገድ እንደላኩት ይናገራል። አሁን ቤትክን ለቀህ ውጣ ተብሎ ህይወቱ አደጋ ላይ ወድቋል:: 

የሳውዲ መንግስት በኦፊሴል እንዲህ አይነት መልክት ያስተላልፍ እንደሆነ የጠየቅነው ጋዜጠኛ፣ መንግስት በቀጥታ እንዲህ አያደርግም ነገር ግን እርሱ ባሰማራቸው ሰዎች አማካኝነት መልክቶችን እንደሚሰድ ይታወቃል ብሎአል።
የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ዘመቻ በማድረግ በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት መታደግ ሲችል በቀን ይህን ያክል ሰው አስመጣሁ በማለት ፕሮፓጋንዳ ይነዛል የሚለው ጋዜጠኛው፣ በሳውዲ የቀረው ኢትዮጵያዊ ወደ አገር ቤት የተመለሰውን በብዙ እጥፍ ይበልጣል ሲል በአገሪቱ ያለውን እውነታ አስረድቷል።
በሌላ በኩል ከሳውድ አረቢያ ወደ የመን የገቡ 3 ሺ ያክል ኢትዮጵያውያን በምግብ እጥረት ተጎሳቁለው እንደሚገኙ እስር ቤት ድረስ በመሄድ ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሀይማኖት ጎብኝቷቸዋል።

Wednesday, November 27, 2013

EU Member of Parliament Ana Gomes in Addis Ababa November


Ana Gomes, known for publicly criticising Ethiopia following the 2005 government crackdown
Serious talk! EU Member of Parliament Ana Gomes, known for publicly criticising Ethiopia following the 2005 government crackdown, which claimed over 200 lives, in a seemingly serious discussion during lunch break with Ethiopian MP and Speaker of the House Abadulla Gemeda in Addis Ababa, November 25, 2013. ANDUALEM SISAY | NATION MEDIA GROUP
The 26th European Union (EU) and African Caribbean Pacific (ACP) Joint Parliamentary Assembly (JPA) opened in Addis Ababa, Ethiopia Monday morning.
The assembly is expected to debate several issues, ranging from use of natural resources to fiscal reform and redistribution of wealth and decentralised cooperation.
The gathering is also expected to discuss respect for the rule of law and the role of an impartial and independent judiciary and South-South and triangular cooperation.
The assembly that will be concluded on Wednesday, has no decision-making powers.
However, it allows elected representatives of ACP countries to address their concerns directly to the EU Commission and be updated on the negotiations on trade deal, such as the Cotonou Agreement.
“There is an ample room for more enhanced partnership in many areas of interest to both sides,” said Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, while opening the assembly.
“But in a large sense, this relationship should not in any way be based on the rather obsolete assumption that one side is the ultimate provider and the other perennial receiver of resources whatever the object of the relationship might be – economic or political.”
JPA comprises 78 members of parliament and 12 vice-presidents from both sides (EU and ACP).
The assembly is expected to be concluded after discussing social and environmental impacts of pastoralism on ACP countries on the last day.
JPA meets twice a year, once in the EU, traditionally in the country holding the presidency of the Council of the EU and once in an ACP country, determined by the group of ACP countries.

Source: AFRICA REVIEW

ሰማያዊ ፓርቲ አፄ ምኒልክ የሞቱበትን አንድ መቶኛ ዓመት በዓል ያከብራል

 
 
 
 
 
 ሰማያዊ ፓርቲ አፄ ምኒልክ የሞቱበትን አንድ መቶኛ ዓመት በዓል እንደሚያከብር የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት አስታውቋል። አፄ ምኒልክ የሞቱበት ዕለት ታህሳስ 3 ቀን በመሆኑ ዕለቱን የፓናል ውይይት፣ ጉብኝትና ኤግዚቪሽኖች በማዘጋጀት በአሉን በልዩ ልዩ ፕሮግራሞች ለማክበር እየተዘጋጁ መሆኑን አስታውቋል።

በዕለቱ በተመሳሳይ ቀን ያለፉት ፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ አብረው የሚታሰቡ መሆኑን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ብርሃኑ ተ/ያሬድ አስታውቋል። ፓርቲው ወደፊትም “የታላቋ ኢትዮጵያ ቀን” በሚል በየሶስት ወሩ ቋሚ ፕሮግራም እንደሚያዘጋጅ ጨምሮ አስታውቋል። አፄ ምኒልክ እና ፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ የሚዘከሩበት ቀን የዚሁ የታላቋ ኢትዮጵያ ቋሚ ፕሮግራም አካል መሆኑንም አመልክቷል።

አፄ ምኒልክንም ሆኑ ፊታውራሪ ኃብተጊዮርጊስ ዲነግዴን መዘከር ያስፈለገው የሀገሪቱን አንድነት ጠብቀው ከማቆየት ባሻገር በሀገሪቱ ዘመናዊነት፣ ቴክኖሎጂ መስፋፋትና እድገት ፈርቀዳጅ በመሆናቸው እንዲሁም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቁሮች በነጮች ላይ ድል እንዲጎናፀፍ ያደረጉ ገናና መሪዎች በመሆናቸው ነው ብሏል።


Monday, November 25, 2013

ግድ የለሹ መንግስት ተብዬው! ከሀና ሰመረ (ኖርዌይ)


የምንሰማውና የምናየው የኛው ከልክ ያለፈ አሳዛኝ ዜና አላስችል ቢለኝ እንደው ትንሽ የውስጤን ሀዘን እና ብሶቴን ቢገልፅልኝ ብዬ ብዕሬን አነሳው::

እኔ የምላቹ እንደው የሰው ልጅ እንዲህ እንዴት ከፋ? አምላክ በራሱ አምሳል የፈጠረውን ሰውን የሚያህል ክቡር ፍጡር ለማጥፋት እንዲህ መሯሯጥ ምን የሚሉት ነው? እኛ ኢትዮጵያኖች ለምን ይሆን እንዲህ በየቦታው ስቃያችን የበዛው? እውነት ግን የምላችሁ ወገኖቼ አያት ቅድመ አያቶቻችን አገራችንን ከወራሪ ጠላት ጠብቀው ያስከበሩ እና እንዳስከበሩ ሲነገር የቆየው የጀብዱነት ታሪክ በደመ ነፍስ በሚወዛወዘው በወያኔ ድርጅት ከስር መሰረቱ ለማፍረስ የታለመ ነው:: ይህንን እኩይ ተግባር በቸልተኝነት መመልከት ከታሪክ አጥፊው ጎራ አብሮ ከመሰለፍ ተለይቶ አይታይም:: ግን እስከመቼ ብለን የጊዜ ቀጠሮ ይዘን ነው አያቶቻችን ደምና አጥንት ከፍለው ባስረከቡን ሀገር ላይ ነፃነታችንን ተነፍገን ተራ እየጠበቅን የስደትን መራራ ፅዋ የምንጎነጨው ግን እስከመቼ? ይህንን ጥያቄዬን ልብ ያለው ለራሱ ይመልስ::

ኢህአዴጋውያንን ሳይሆን በመላው አለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ያሳዘነና ያስቆጣው በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርሰውን በርካቶችን እስከ ሞት ፤ ሴት እህቶቻችንን እስከ መደፈር ፡ እንዲሁም ወንድሞቻችንን ለከፍተኛ ድብደባ ከዳረገውም በላይ የህወሀት አባላት በሳውዲ አረቢያ ልጅም ዘመድም ስለሌላቸው ወገኖቻችንን ካሉበት ችግር ለማውጣት የተከፈለ አመርቂ እንቅስቃሴ የለም:: እንዲያውም በተገላቢጦሽ አረቦቹ በመለስ ዜናዊ ለ60 ዓመት ሊዝ የሰጣቸውን መቶ ሺህ ሄክታር የኢትዮጵያውያኑ መሬት ላይ ህይወታቸውን ላጠፉ ፤ ሰብዓዊ መብታቸውን ለገፈፉ ፡ እንዲሁም ደማቸውን ላፈሰሱት ለሳውዲ አረቢያ ህዝብ ቀለብ ሩዝ እያመረቱ ነው::

ይህም አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያኖች ፍትህን ፍለጋ በተሰደዱበት ዓለም ሁሉ በሙሉ ነፃነት የወገኖቻቸውን በደል እልህ በተሞላበት ተቃውሞ ሲያሰሙ ፤ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ከአይቤክስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የተቃውሞ ድምፃቸውን ሊያሰሙ የተሰበሰቡትን በተወለዱበት እና በገዛ ሃገራቸው የወገኖቻቸውን ስቃይ እንዳይቃወሙ በፖሊስ የመባረርና ከፊሉም ለእስር ተዳርጓል::

ግን ማን ይሆን ስደትን ሐሴት አድርጎ ቀዬውን ጥሎ በባዕድ ሀገር የሚንከራተት? ፍትህ ቢጓደልበት፤የብልሹ አስተዳደር ግፍና የጭቆና ቀንበር ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት እንጂ፤ ለዚህ ሁሉ ችግሮች ተጠያቂው ለዜጎቹ ህልውናና ክብር ግድ የለሽ የሆነው መንግስት ተብዬው ነው:: ለነገሩ ወያኔ ብዙ ትንንሽ አድርጎ ከፋፍሎ የወሰነውን እኛ ካላፈራረስነው ችግራችንም ማብቂያ አይኖረውም የወያኔም አላማ ግብ ይመታለታል ስለዚህ ወገኖቼ “ህዝብ መንግስትን ሳይሆን መንግስት ህዝብን” አገልጋይ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት እንዲሁም ለዚህ ያበቃንን ስርዓት ለማስወገድ ድክመታችንን በጋራ መፍታት የትግሉ ቅድመ ሁኔታ መሆን አለበት::

ኧረ ማንን ይሆን እንክርዳዱን ከስንዴው አንጓሎ እንዲያስወግድልን የምንጠብቀው?


ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

Such inhuman and shameful treatment of Ethiopian migrants living in Saudi Arabia and other Gulf States should be stopped immediately. by Garbis Korajian

 
I am a fourth generation Ethiopian-Armenian and, like many Armenians who lived in Ethiopia, my grandparents took refuge in Ethiopia after the Armenian Genocide. Those Armenians who were fortunate enough to have escaped the Turkish atrocities and mass murders of the early 20th century repatriated to different countries around the world. Ethiopia was a country that provided unconditional support and welcomed Armenians with open arms. We lived and prospered in Ethiopia where we maintained our institutions such as our churches, schools and community centers without any interference from the Government of Ethiopia and its citizens. We were treated as brothers and sisters and lived a good life. Although I now live in Canada, I still have a lot of love for Ethiopia and the people.
Therefore, I find it necessary to say a few words about the current mistreatment of Ethiopians in the Gulf States including Saudi Arabia which has been the focus of despicable mistreatment of Ethiopians. For various reasons, mostly economic, today’s young Ethiopians are traveling abroad looking for better opportunities of life through employment. For women, this is mostly domestic help and for men, it would be construction or any other job they can find. Needless to say, life for Ethiopians looking for work and to survive in these countries is not easy. On top of these hardships, the Ethiopians who are law abiding and hard working members of society are facing persecution beyond anyone’s imagination. There is no justification for such cruel behavior.
It is important to remember that one day, the citizens and its descendants from the countries that are committing such atrocities on helpless Ethiopians may very well seek refuge in Ethiopia as was done 1500 years ago. As always, what goes around always comes around. Do not forget your history vis-a-vis Ethiopia and stop mistreating our Ethiopian brothers and sisters living in your country. Start treating them with decency and respect.
 
SOURCE, ABUGIDA

Saturday, November 23, 2013

Overrakte brev til ordføreren

 
...
INTERNASJONAL SOLIDARITET. Lomita Baheru overrekker ordfører John Opdal et brev som skal sendes til den norske regjeringen. Foto: Ernst Olsen
 
Flyktninger og asylsøkere fra Etiopia og Eritrea overrakte ordfører John Opdal et brev som forteller om den vanskelige situasjonen til landsmenn bosatt i Saudi-Arabia.
Ernst Olsen
 


Lørdag 16. november var flyktninger og asylsøkere fra Etiopia og Eritrea samlet i Odda sentrum.
De minnet ofrene etter alle de grufulle overgrepene mot deres landsmenn i Saudi-Arabia den siste tiden.
 
Dette er en hendelse som i norske medier har havnet litt i skyggen av den tragiske naturkatastrofen på Filipinene.
 
Onsdag fikk gruppen fra Etiopia og Eritrea presentere sitt budskap for Odda kommunestyre.
Ordfører John Opdal fikk overrakt et brev der det settes fokus på overgrepene mot deres landsmenn i Saudi-Arabia, de skriver også om gjentatte brudd på menneskerettighetene i sitt eget hjemland.
Gruppen av flyktninger, som satt på galleriet, ba ordføreren videresende brevet til den norske regjeringen.
 
- Vi takker lokalpolitikerne i Odda for at vi fikk slippe til, og håper de vil støtte oss i det videre arbeidet, sa Lomjta Baheru som overrakte brevet.
 
SOURCE,normal_logo.gif