Monday, October 28, 2013

እሳት አስነሳችሁ በሚል እስሩ ቀጥሏል

ኢህአዴግ የዘራውን አጨደ፣ ተጠያቂው ማን ነው?

fire

በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ተቃውሞ ቢያቀርቡም የኢህአዴግን ጆሮ ማግኘት ያልቻሉ ተበዳዮች ርምጃ ወሰዱ። ሕዝብ ወዶና ፈቅዶ ያልተቀበለው ኢንቨስትመንት ከዘረፋ ተለይቶ እንደማይታይ የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቀዋል። ውድመት የደረሰበት የህንድ ኩባንያ በልማት ባንክ ላይ ኪሳራ ሊያስከትል እንደሚችል ስጋት አለ። ለደረሰው ጉዳት “ተጠያቂው ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ተነስቷል። በጥርጣሬ የሚታሰሩ መበራከታቸው በክልሉ ባሉ ተመሳሳይ የእርሻ ኢንቨስትመንት ባለቤቶችን ስጋት ላይ ጥሏል።
ሻይ ቅጠል ለማልማት የተፈጥሮ ጥብቅ ደን እንዲያወድም የተፈቀደለት ቬርዳንታ ሀርቨስት የተባለ ኩባንያ በከፍተኛ ወጪ ያለማውና ለመለቀም በደረሰ ምርት ላይ ማንነታቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች እሳት ለቀውበታል። ጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓም ደረሰ በተባለው ቃጠሎ ኩባንያው የደረሰበት ሊሳራ እስከ 80 ሚሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ስለ ጉዳዩ የሚያውቁ አስታውቀዋል።
አንጋፋ እድሜ ጠገብና ረዣዥም የተፈጥሮ ደን በመጨፍጨፍ ጣውላ እያመረተ ሲቸበችብ የነበረው ኩባንያ ሙሉ ንብረቱና ከፍተኛ መጠን ያለው የጣውላ ምርት ከተለያዩ ማሽኖች ጋር ወድሞበታል። የአካባቢው የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት ኩባንያው ላይ የደረሰው የእሳት ቃጠሎ ለመሰብሰብ የደረሰውን የሻይ ቅጠል ማሳ አጋይቶታል።
በጋምቤላ ክልል በመዠንግር ዞን፣ በጎደሬ ወረዳ በጉማሬና በካቦ ቀበሌዎች የሚገኝ 5000 ሄክታር በደን የተሸፈነ መሬት በኢንቨስትመንት ስም እንዲሸጥ መወሰኑን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ተቃውሞ አሰምተው ነበር። በወቅቱ ውሳኔውን “በባዕድ ወራሪ ሃይል እንኳን የማይፈጸም” በማለት የተቹና ቅሬታቸውን የገለጹ ነበሩ።
ሙሉ በሙሉ በደን የተሸፈነ 3012 ሄክታር ድንግል ለም መሬት በሄክታር111 ብር ሂሳብ ለ50 ዓመት የሊዝ ኮንትራት የተሸጠለት ይህ ኩባንያ ጥብቅ ደኑን ከማውደሙ በፊት ውሳኔው እንዲጤን የአካባቢው ህዝብ በወኪሎቹ አማካይነት ለፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ጥያቄ አቀርበው ነበር። በወቅቱ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ድርጊቱን በመቃወም የሚከተለውን ጽሁፍ አትሞ ነበር። ሰሚ ባለመገኘቱ የተፈራው ደረሰ።
ጡረተኛው ፕሬዚዳንት ለአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በሰጡት ትዕዛዝ መሰረት የተፈጥሮ ደኑ ከመጨፍጨፉ በፊት ውሳኔው እንዲመረመርና እንዲጠና ሚያዚያ 28 ቀን 2002 ዓ ም ለክልሉ ደብዳቤ ልኮ ነበር። ሟቹ ጠ/ሚኒስትር በወቅቱ የአፍሪካ የተፈጥሮ ጥበቃና የአየር ንብረት ተሟጋች ነኝ ያሉበት ወቅት መሆኑንን በማስታወስ፣ የፕሬዚዳንቱን መመሪያ በመጠቆም ባለስልጣኑ የጻፈውን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ የክልሉ ፕሬዚዳንት ህዳር 10 ቀን በተጻፈ ደብዳቤ ደመሰሱት። ከላይ የተጠቀሰው ኩባንያ የ50 ዓመቱን ውል ቅድሚያ ክፍያ የአንድ ዓመት 19 ሺህ ዶላር ስለከፈለ ቦታውን እንዲረከብ ዞኑንን አዘዙ።
የበላይና የበታቹ በማይታወቅበት የመለስ አወቃቀር ጥብቅ ደኑ ያለበት መሬት ለህንዱ ኩባንያ ተላለፈ። ህዝብ ያነሳውን ጥያቄ እስከ ፕሬዚዳንቱ ያደረሱት ሊቀመንበር እንደ ወንጀለኛ ተቆጥረው ከሃላፊነታቸው ተባረሩ። ህዝብ የኑሮው መሰረትና የህይወቱ ያህል የሚንከባከበው ደን ተጨፈጨፈ። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ደኑ ሲጨፈጨፍ የነበረው ሃዘን በቃል የሚገለጽ አልነበረም።timber log
ባገኘው ከፍተኛ የደን ምርት ጣውላ ማምረት የጀመረው ኩባንያ መጋዘን ገንብቶ የጣውላ ንግድ ውስጥ ገባ። አሁን ድረስ ንዴቱና የበደል ስሜቱ ያለቀቀቃቸው የአካባቢው ነዋሪዎች የተካሄደባቸውን ግፍ “ዝርፊያ” እያሉ ነው የሚጠሩት።
ህግን ጠብቀው ኢህአዴግን ያሳሰቡት የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ቢሆን በእስርና በድብደባ በማሰቃየት ኢንቨስትመንትን /ነዋሪዎቹ ዝርፊያ ነው የሚሉት/ በክልሉ ቀጣይ ማድረግ አይቻልም። አስቀድሞ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ኢህአዴግና ኩባንያው ጆሮ ሰጥተዋቸው ቢሆን ኖሮ እንዲህ ያለ አደጋ ሊፈጠር እንደማይችል አስተያየት ሰጡ አሉ።
92 ሚሊዮን ብር በላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እዳ ያለበት የእርሻ ድርጅት፣ ንብረቱ በእሳት ከወደመ በኋላ የተሸከመው እዳ አጀንዳ ሆኗል። የደረሰበት ውድመት ከፍተኛ በመሆኑ ክልሉንና ኢህአዴግን ካሳ እንደሚጠይቅም ከወዲሁ ተሰምቷል። ዜናውን ያቀበሉ ክፍሎች “ህዝብ ላልተቀበለው ኢንቨስትመንት ካሳና የልማት ባንክ ላይ ለደረሰው ኪሳራ ተጠያቂው ኢህአዴግ ነው” የሚል ጥያቄ መነሳቱን አመልክተዋል።
ለአበባ እርሻ ላስቲክና ኬሚካል በማስያዝ ልማት ባንክን እያለቡ የተሰወሩ በርካታ ድርጅቶችና ለስርዓቱ ቅርበት ያላቸው ሸሪኮቻቸው መኖራቸውን በማስታወስ በጋምቤላ ተመሳሳይ ድርጊት ሊፈጸም እንደሚችል የዜናው ምንጮች ጠቁመዋል። ካራቱሪ በኪሳራ መንገዳገዱን፣ ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ በ”ውክልና” ለሳዑዲ አረቢያ ቀለብ እንዲያመርት የተከሉት ሳዑዲ ስታርና ሌሎች የህወሃት ሰዎች ከተለያዩ የአገር ውስጥ ባንኮች ከፍተኛ ገንዘብ መበደራቸውን ገልጸዋል።
“ህዝብን ያለፈቃዱ በማፈናቀልና መሬቱን በመቀማት የሚከናወን ኢንቨስትመንት ሁሌም አደጋ ላይ መሆኑ አያጠራጥርም” በማለት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ አኢጋን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ለጎልጉል ገልጸዋል። “ኢንቨስትመንት እንኳን ደህና መጣህ በሚል ህዝብ ካልተቀበለው ዘረፋ ነው” ያሉት አቶ ኦባንግ “በሰላማዊና በሰለጠነ መንገድ ድምጹን ሲያሰማ ጆሮ ያጣ ህዝብ ተቃውሞውን ገለጸ” በማለት በደረሰው ውድመት ባይደሰቱም ለውድመቱ ተጠያቂው ኢህአዴግና ከኢህአዴግ ጋር ተሻርኮ ዝርፊያ ያከናወነው ድርጅት እንደሆነ አመልክተዋል።
ካሩቱሪና ሳዑዲ ስታርን ጨምሮ ህዝብ ላይ በተፈጸመ ግፍ ሃብት ለማፍራትና ለመበልጸግ የሚያስቡ ትልቅ ግንዛቤ ሊወስዱ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ ኦባንግ “ኢህአዴግ ዝርፊያና ኢንቨስትመንትን ለይቶ መሔድ ካልቻለ ስጋቱ እየጨመረ ይሄዳልና ከስህተት በመመለስ ህዝብ በሚፈቅደው መልኩ ማስተናገድ ግድ ነው” ሲሉ አሁንም ጆሮ የለውም ለሚባለው ኢህአዴግ ማሳሰቢያ አዘል ምክር ለግሰዋል። ባለሃብት የሚባሉትም ከዚህ ታላቅና አሳዛኝ ውድመት ሊማሩና ህዝብ “እንኳን ደህና መጣችሁ እንዲላቸው ህዝብ ከሚቃወመው ዝርፊያና አሰራር ራሳቸውን ሊያገሉ ይገባል” ብለዋል።
የክልሉ ፕሬዚዳንት ቃጠሎውን ማመናቸውን ሪፖርተር በእሁድ እትሙ ያስታወቀ ሲሆን አጣሪ ኮሚቴ ተቃቁሞ አደጋውን ያደረሱት እነማን ናቸው የሚለው እየተመረመረ እንደሆነ ጠቁሟል። የክልሉ የጎልጉል ምንጮች በርካታ ሰዎች እሳት አስነስታችኋል በሚል መታሰራቸውና በፌዴራል አንጋቾች እየተመረመሩ መሆኑን አረጋግጠዋል። እሳት ያስነሱትን ለማጋለጥ በሚል በየመንደሩ በሚደረግ ማዋከብ ነዋሪዎቹ መማረራቸውን ተናግረዋል። ለጊዜው የእስረኞች ቁጥር ባይታወቅም ወደ ማዕከል የተላኩ በርካታ እንደሆኑም ገልጸዋል። በማያያዝም ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ኢህአዴግም ሆነ ማንም ተጠቃሚ ስለማይሆን ህዝብን ማዳመጥ ሊቀድም እንደሚገባው ጠቁመዋል።

Sunday, October 27, 2013

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢሕአዴግ በተቃዋሚዎች ደካማነት ድርብ ኃላፊነት ተሸክሟል አሉ


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢሕአዴግ በተቃዋሚዎች ደካማነት ድርብ ኃላፊነት ተሸክሟል አሉ

-ፓርላማው መንግሥትን እንዲቆጣጠር ጠየቁ
-አፈ ጉባዔ አባዱላ ፓርላማው እንደማያወላዳ ጠቆሙ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ሐሙስ የአስፈጻሚውን መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት አዳራሽ ጠርቶ ንግግር እንዲያደርጉ የተጋበዙት
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎች ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው ምክንያት ብቸኛው አውራ ፓርቲ ለመሆን መገደዱን ገለጹ፡፡ 
በዚህም የተነሳ ገዢው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንደወደቀበትና ይህንን ኃላፊነትም በአግባቡ ከመወጣት ባሻገር አማራጭ ባለመኖሩ ፓርቲው የመሠረተው መንግሥት በርካታ ሥራ ተደቅኖበታል ብለዋል፡፡ ይህንንም ኃላፊነት ለመወጣት አስፈጻሚ አካላት ለሕገ መንግሥቱ ታማኝ በመሆን ሥራቸውን ለሕዝቡ ግልጽ ማድረግ አለባቸው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ በመሆኑም የመንግሥትን እንቅስቃሴ የመቆጣጠር ሥልጣን ያለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ ቁጥጥርና ክትትል በአስፈጻሚው መንግሥት ላይ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ 
ፓርላማው በተጠናቀቀው 2005 ዓ.ም. ግርምትን የጫረ ቁጥጥርና ክትትል በአስፈጻሚው መንግሥት ላይ መጀመሩ ይታወሳል፡፡ በተጠቀሰው ዓመት ለፓርላማው የቀረበው የዋናው ኦዲተር ሪፖርት መንግሥት በ2004 ዓ.ም. ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ለብክነት መዳረጉንና ለምን ዓላማ እንደዋለ ማወቅ አለመቻሉን ገልጾ ነበር፡፡ ዋናው ኦዲተር ያቀረበው ሪፖርት ከዚህ ቀደም ከነበሩት ዓመታት የተለየ ባይሆንም ፓርላማው ግን የተለየ ትኩረት በመስጠት ግድፈት ፈጽመዋል የተባሉ ተቋማት ኃላፊዎችን በመጥራት ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፡፡ 
በዓመቱ መጨረሻ ላይ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የቀረበውን የ2006 በጀት መመልከት ሲጀምርም ተመሳሳይ ማሳሳቢያ በመስጠት በጀቱን በአግባቡ የማይተገብሩ መሥሪያ ቤቶችን ባለመቆጣጠር ሚኒስቴሩን ተጠያቂ እንደሚያደርግ አጥብቆ መግለጹ፣ ዋና ከተባሉት አስገራሚና ድንገተኛ የፓርላማው የለውጥ እንቅስቃሴ ተጠቃሽ ነው፡፡ 
ፓርላማው ባለፈው ዓመት ያደረገውን ጠንካራ ቁጥጥር ከመጀመሩ በፊት በዚህ ሳምንት መጨረሻ እንዳደረገው፣ አስፈጻሚውን መንግሥት በመሰብሰብ የተለየ ቁጥጥር ለማድረግ መነሳቱን አስታውቆ ነበር፡፡ 
ባለፈው ሐሙስ የተደረገውም ስብሰባ የዚሁ አካል እንደሆነ በውይይቱ ላይ የተገኙ የምክር ቤት አባላት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ፓርላማው አስፈጻሚውን ከመጥራቱ በፊት ለአምስት ቀናት በራሱ ቅጥር ግቢ ዝግ ስብሰባ ማድረጉን የገለጹት ምንጮች፣ ዘንድሮ ከተለመደው የቁጥጥርና የክትትል ሥራ የተለየ አሠራር ለመፍጠርና ተግባራዊ ለማድረግ እንደወሰነ አስረድተዋል፡፡ 
ፓርላማው መንግሥትን የሚቆጣጠርበትና የተለመደ የተባለው አሠራር የአስፈጻሚው መንግሥት ተቋማት ኃላፊዎች በዓመት ውስጥ ቢበዛ ሁለት ጊዜ ለፓርላማው የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን እንዲያቀርቡ ማድረግ ነው፡፡ 
ፓርላማው ዘንድሮ እንደ አዲስ ለመተግበር ያቀደው የቁጥጥርና ክትትል አሠራር ግን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን የማዳመጥ ትኩረት እንደማይኖረው ምንጮች ተናግረዋል፡፡ በርካታ ገጾችን የያዙ እርባና የሌላቸው ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ከማዳመጥ ይልቅ፣ የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴዎች ለይተው በሚያቀርቧቸው አስፈላጊ ጉዳዮች ላይ ብቻ የተቋማት ኃላፊዎች ሪፖርት እንዲያደርጉና ፓርላማውም በማስረጃ ላይ የተደገፈ ክርክር ውስጥ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ 
ይህንን የፓርላማውን አሠራር ሪፖርት የማድረግ ግዴታ ላለበት ሕግ አስፈጻሚው ለማስተዋወቅ በምክር ቤቱ በተጠራው ስብሰባ ላይም ይፋ መደረጉን ምንጮች አስረድተዋል፡፡ ስብሰባው እንዲከፍቱ የተጋበዙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ ፓርላማው በአስፈጻሚው ላይ ጠንካራ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባው ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም ከጀመረው አሠራር በላቀ ሁኔታ ቁጥጥር ማድረግ ቢችል ለአገሪቱ የዲሞክራሲ ግንባታ ቁልፍ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
‹‹በአገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት መጠናከር የሚጠበቅባቸውን ሚና ባለመወጣታቸው፣ ገዥው ፓርቲ ብቸኛ አውራ ፓርቲ በመሆን ድርብ ኃላፊነቶችን ለመሸከም ተገዷል፤›› ማለታቸውን ውይይቱን የተከታተሉት ምንጮች ገልጸዋል፡፡
‹‹የአገሪቱ ሕዝቦች በአሁኑ ወቅት ሌላ አማራጭ ፓርቲ የላቸውም፤›› በማለት በንግግራቸው የቀጠሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹የወደቀብንን ኃላፊነት ለመወጣት አስፈጻሚው መንግሥት ለሕገ መንግሥቱና ለሕዝቦች ታማኝ በመሆን፣ እንዲሁም እያንዳንዱን እንቅስቃሴ ለሕዝብ ግልጽ ማድረግ ይጠበቅበታል፤›› ማለታቸውን ምንጮች አክለዋል፡፡ አስፈጻሚው የመንግሥት አካላት የሚያወጧቸው መመርያዎችና ደንቦች ፓርላማው ከሚያወጣቸው ሕጎች ጋር እንዳይጣረሱ መጠንቀቅ እንዳለባቸው አስረድተዋል፡፡ 
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት አፈ ጉባዔ አባዱላ ገመዳ ፓርላማው የማያወላዳ ቁጥጥር በአስፈጻሚው ላይ እንደሚያደርግ ጠቁመው፣ የአስፈጻሚው መንግሥት ኃላፊዎች ከወዲሁ ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ 
SOURCE, REPORTER

Wednesday, October 23, 2013

ብረታ ብረት ኮርፖሬሽንና ሚድሮክን ጨምሮ 20 ድርጅቶች እንዳይፈተሹ ያደረጉ ከፍተኛ የሙስና ተጠርጣሪዎች ተከሰሱ



ብረታ ብረት ኮርፖሬሽንና ሚድሮክን ጨምሮ 20 ድርጅቶች እንዳይፈተሹ ያደረጉ ከፍተኛ የሙስና ተጠርጣሪዎች ተከሰሱ

አቶ መላኩ ፈንታ የሦስት ልጆች እናትን አፋተው አግብተዋል ተባለ 
-አቶ ጌቱ ገለቴን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌሉበት ክሳቸው ተሰማ
በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ከግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. መጀመሪያ ጀምሮ በቁጥጥር ሥር ውለው ነሐሴ 22 ቀን 2005 ዓ.ም. ክስ ተመሥርቶባቸዋል የተባሉት
ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ተጠርጣሪዎች፣ የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንና ሚድሮክን ጨምሮ 20 ድርጅቶች ከውጭ ዕቃ ሲያስመጡ እንዳይፈተሹ አድርገዋል በሚልና በተለያዩ የሙስና ድርጊቶች የተካተቱበት የክስ ቻርጅ፣ ጥቅምት 11 እና 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ከአንድ ወር ከ15 ቀናት ቆይታ በኋላ ተነበበላቸው፡፡ 
ክሱን የመሠረተው የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ሲሆን፣ በተለያዩ ሦስት የክስ መዝገቦች በድምሩ በ55 ተጠርጣሪዎችና በአምስት ድርጅቶች ላይ ያዘጋጀውን የክስ ቻርጅ፣ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት አቅርቦ አሰምቷል፡፡
የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንደዘረዘረው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታ፣ የሕግ ማስከበር ሥራዎች ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ፣ የአዳማ ቅርንጫፍ የሕግ ማስከበር ኃላፊ አቶ ተመስገን ሥዩም፣ የአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ የሕግ ማስከበር ኃላፊና በሚሌና አካባቢው ያሉ ፍተሻ ጣቢያዎች ሥራ አስኪያጅ አቶ እሸቱ ግረፍና የአዳማ ቅርንጫፍ የፍተሻ ክፍል ኃላፊና አጠቃላይ የቅሬታ ቡድን አስተባባሪ አቶ ያለው ቡላ በዋና ወንጀል አድራጊነትና የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኋን በመምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡
እንደ ኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ገለጻ፣ ባለሥልጣናቱና ኃላፊዎቹ በመንግሥትና በሕዝብ በተጣለባቸው ከፍተኛ ኃላፊነት የመንግሥት ግብር እንዲሰበሰብ ማድረግ ሲገባቸው፣ በተቃራኒው በመሥራት የመንግሥት ቀረጥና ታክስ እንዳይከፈል አድርገዋል፡፡ የተከለከሉ ዕቃዎች እንዳይገቡ በፍተሻ የሚለይበት ሥርዓት እንዳይፈጠር አድርገዋል፡፡ ሕገወጥ አስመጭዎች እንዳይጠየቁ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እንዲመቻች በማድረግ ድርጅቶች (አስመጪዎች) ተመርጠው ሳይፈተሹ እንዲያልፉ አድርገዋል፡፡ የተለያዩ አስመጭዎችና ትራንዚተሮች ሕገወጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጉቦና ተገቢ ያልሆነ ጥቅም የመቀበል፣ የመስጠትና የማቀባበል ወንጀል እንዲፈጽም ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠራቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ 
ከአቶ መላኩና ከአቶ ገብረዋህድ፣ ለባለሥልጣኑ የሚሌ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅና በሚሌ ቅርንጫፍ ሥር የሚገኙትን የጋላፊ መቆጣጠሪያ ጣቢያ፣ የሰመራ ደረቅ ወደብ ጣቢያ፣ የሚሌ የዘመናዊ ማሽን መፈተሻ ጣቢያና የአዋሽ መቆጣጠሪያ ጣቢያ አስተባባሪ አቶ እሸቱ ግረፍ ትዕዛዝ ይተላለፍላቸው እንደነበር ክሱ ይገልጻል፡፡ 
በትዕዛዙ መሠረት ከ2003 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ የትራንዚት ፈቃድ ተሰጥቷቸው በጂቡቲ ወደብ በኩል ከውጭ አገር የሚገቡ ዕቃዎች ሚሌ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ሲደርሱ በአቶ እሸቱ ግረፍ አማካይነት ተመርጠው ሳይፈተሹ ‹‹ተፈትሸዋል›› የሚል ማረጋገጫ እየተሰጣቸው ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ መደረጋቸውን፣ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡ 
ሳይፈተሹ ‹‹ተፈትሸዋል›› የሚል ማረጋገጫ እየተሰጣቸው ቀረጥና ታክስ ሳይከፍሉ የተለያዩ ዕቃዎችን ወደ አገር ውስጥ ያስገቡት ድርጅቶች ኒያላ ሞተርስ የመኪና መገጣጠሚያና መለዋወጫ ዕቃ አስመጪ፣ ፔትራም፣ ሞኤንኮ፣ ጌታስ ትሬዲንግ፣ አልሳም፣ ብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ አይካ አዲስ (የቱርክ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ)፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጅነሪንግ፣ ሆላንድ ካርስ (ከስሮ ተዘግቷል)፣ ቶታል ኢትዮጵያ፣ ሚድሮክ፣ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን፣ ድሬ ኢንዱስትሪያል ትሬዲንግ፣ ኢትዮ ሌዘር፣ ኢትዮ ቆዳ ፋብሪካ፣ ባሰፋ ትሬዲንግ፣ ነፃ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ጌታስ ኢንተርናሽናልና ኮሜት ትሬዲንግ መሆናቸው በክሱ ተዘርዝረዋል፡፡ 
አቶ ጌቱ ገለቴ የጌታስ ትሬዲንግና ጌታስ ኢንተርናሽናል ባለቤት (በሌሉበት)፣ አቶ ገብረ ሥላሴ ገብሬ (የኮሜት ትሬዲንግ ሀውስ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ) አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር (የባስፋና ነፃ ትሬዲንግ ባለቤት)፣ አቶ ከተማ ከበደ (የኬኬ ድርጅት ባለቤት) ከነድርጅቶቻቸው በክሱ ውስጥ የተካተቱ ሲሆኑ፣ ከላይ የተዘረዘሩት ድርጅቶችም ሆኑ ባለቤቶቻቸው በክሱ አልተካተቱም፡፡ አቶ ጌቱ ገለቴ ከአቶ መላኩና ከአቶ ገብረዋህድ ጋር ባላቸው ግንኙነት ወደ አገር ውስጥ የተለያዩ ዕቃዎችን ሲያስገቡ በሕግ አግባብ መሠረት ተፈትሸው ተገቢውን ታክስና ቀረጥ መክፈል ሲገባቸው፣ በሕገወጥ ትዕዛዝ አማካይነት ዕቃዎቻቸው ሳይፈተሹ ‹‹ተፈትሸዋል›› የሚል የማረጋገጫ ኢንቮይስ ተስተናግደው ሕገወጥ ጥቅም ማግኘታቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ 
ጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. በተነበበው ክስ ውስጥ 31 ተጠርጣሪዎች የተካተቱ ሲሆን፣ ባጠቃላይ 28 ክሶች ቀርበዋል፡፡ በክሶቹ ውስጥ በዝርዝር በተገለጹት በባለሥልጣኑ መሥሪያ ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎችና ከ20 በላይ የሚሆኑ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችና ዋና መሥሪያ ቤት ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎችና ከውጭ ድርጅቶች ጋር በመመሳጠር በተለያዩ ቦታዎች ጉቦ የተቀበሉ መሆኑን፣ በፍተሻ ወቅት እንደተፈተሸ አድርጎ በማሳለፍና የተሳሳተ ሰነድ በመጠቀም በመንግሥትና በሕዝብ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ፣ የመንግሥትን ሥራ በማያመች መልኩ በመምራትና በዋና ወንጀል አድራጊነትና የሙስና ወንጀል በመፈጸም ክስ ተመሥርቶባቸዋል፡፡ 
በሦስቱም የክስ መዝገቦች ላይ ተጠርጥረው ስማቸው የተጠቀሰው አቶ መላኩ ፈንታና አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም. በተነበቡ ሁለት የክስ መዝገቦች ላይም የመጀመሪያው ተጠሪ ሆነው ተከሰዋል፡፡ 18 ሰዎች የተካተቱበት የክስ መዝገብ የባለሥልጣኑ ከፍተኛ ሹማምንትና ኃላፊዎች የተካተቱበት ሲሆን አቶ አመሐ ዓባይ፣ አቶ ነብዩ ሳሙኤል፣ አቶ አስፋው ወሰን አለነ፣ አቶ ተስፋዬ መርጊያ፣ አቶ አማረ ገብረወልድ፣ አቶ መስፍን አህመድ፣ አቶ ደሜ አበራ፣ አቶ ተስፋዬ ቤተና ወ/ሮ ሃይማኖት ዓለሙ የተባሉ ተጠርጣሪዎች በክሱ የተካተቱ ቢሆንም ክሱ የተሰማው በሌሉበት ነው፡፡ 
አቶ መላኩ፣ አቶ ገብረዋህድ፣ የባለሥልጣኑ የኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በላቸው በየነና በሌሉበት የተከሰሱት የባለሥልጣኑ ኃላፊዎች የተጠረጠሩበትን የሙስና ወንጀል የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ እንደገለጸው፣ ከታክስ ገቢ ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ማስተናገድ የሚያስችሉ አዋጆችና አጣሪ ኮሚቴ ቢኖርም፣ አቶ መላኩ በአዋጁ መሠረት የቀረቡ አቤቱታዎችን እንደገና መከለስ የሚያስችል ሕገወጥ ኮሚቴ አቋቁመዋል፡፡ ሕገወጥ ድርጊቱን መፈጸም የሚያስችል መመርያም አውጥተዋል፡፡ በዚህም መሠረት ሀዋስ አግሮ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተባለ ድርጅት በሕገወጡ መመርያ መሠረት አቤቱታ እንዲያቀርብ በማድረግና ሕገወጡ ኮሚቴ እንዲያየው በማድረግ ከ22.3 ሚሊዮን ብር በላይ መንግሥት እንዲያጣ ማድረጋቸውን ክሱ ይተነትናል፡፡ አቶ ገብረዋህድም ለዚሁ ድርጅት በሕገወጥ መንገድ ድጋፍ በማድረግና ካልተያዙት ተጠርጣሪዎች (የሕገወጥ ኮሚቴ አባላት ናቸው) ጋር በመተባበር የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኋን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡
ሼባ ስቲል ሚልስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የንግድ ትርፍ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስና  ከተከፋዩ ሒሳብ የሚቀነስ ግብር ኦዲት ተደርጎ 101.4 ሚሊዮን ብር እንዲከፍል ከተወሰነበት በኋላ፣ ለሕገወጡ ኮሚቴ አቤቱታ እንዲያቀርብ በማድረግ፣ አቶ ገብረዋህድ እንዳይከፍል ማድረጋቸውን ክሱ ይጠቅሳል፡፡ ለሌሎችም በርካታ ድርጅቶች ላይ ግብር እንዳይሰበሰብ ማድረጋቸውን ክሱ በዝርዝር ያብራራል፡፡ 
17 ክሶችን በያዘው መዝገብ ውስጥ አቶ መላኩ ፈንታ የሦስት ሕፃናት እናትን ከትዳራቸው በማፋታት እንዳገቧት የሚገልጽ ክስም ተካቷል፡፡ የዓቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያብራራው፣ አቶ ደምሴ ዓለማየሁና ወ/ሮ መቅደስ ለማ ከኅዳር 8 ቀን 1993 ዓ.ም. ጀምሮ ተጋብተው ይኖሩ ነበር፡፡ ሦስት የዘጠኝ፣ የአምስትና የሁለት ዓመት ሕፃናትንም አፍርተዋል፡፡ ወ/ሮ መቅስና አቶ ደምሴ ሳንክቹሪ ኢንተርናሽናል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የተባለ ድርጅት አቋቁመው እስከ 2001 ዓ.ም. ድረስ ሠርተዋል፡፡ በ2001 ዓ.ም. አቶ ደምሴ ግብር ለመክፈል ሲሄዱ 144,000 ብር እንዲከፍሉ ይነገራቸዋል፡፡ ግብሩ የበዛባቸው አቶ ደምሴ ቅድሚያ ይከፍሉና ለምሥራቅ አዲስ አበባ የጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አቤቱታ ያቀርባሉ፡፡ ጉዳዩ መፍትሔ ሳያገኝ ከአንድ ዓመት በላይ በመፍጀቱ ባለቤታቸው ወ/ሮ መቅደስ ለቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ያቀረቡትን አቤቱታ ለአቶ መላኩ በግልባጭ ሊሰጡ ወደ ቢሮአቸው ያመራሉ፡፡ አቶ መላኩ በወቅቱ የነበራቸውን ሥልጣን መከታ በማድረግ በሚያዝያ ወር 2002 ዓ.ም. አካባቢ ከተገመተባቸው ግብር ላይ 100 ሺሕ ብር እንዲቀነስ ማድረጋቸውንና ወ/ሮ መቅደስን ማማገጥ መጀመራቸውን፣ በተለያዩ ጊዜያት በሾፌራቸው አማካይነት ወደ ባህር ዳር በመውሰድ ሰመርላንድ ሆቴል ለሦስትና ለሰባት ቀናት መቆየታቸውን፣ እንዲሁም በመንግሥት ተሽከርካሪና ነዳጅ በመጠቀም ሴትየዋን ሲያዝናኑ መክረማቸውን ክሱ ዘርዝሯል፡፡ በመጨረሻም ወ/ሮ መቅደስን ከትዳራቸው በማፋታትና ልጆቻቸውን ያለአሳዳጊ በመበተን አግብተዋቸዋል፡፡ በመሆኑም በፈጸሙት የማፋታት፣ ልጆችን ያለ አሳዳጊ እንዲቀሩ የማድረግና በፈጸሙት የሥልጣን አላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል መከሰሳቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡
በአጠቃላይ የባለሥልጣኑ መሥሪያ ቤት ሹማመንትና ኃላፊዎች ግብር እንዳይሰበስብ በማድረግ፣ በመቀነስ፣ ፍተሻ እንዳይኖር በማድረግ፣ በተለያየ ቦታ መጠኑ የተለያየ ጉቦ በመቀበልና ሥልጣንን ያላግባብ መጠቀም የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመጨረሻ ያነበበውና 93 ክሶችን ያካተተው የክስ መዝገብም ከአቶ መላኩ፣ ከአቶ ገብረዋህድና ባለቤታቸው ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋዬ በተጨማሪ፣ ምክትል ዋና ዓቃቤ ሕግ የነበሩትን አቶ መርክነህ ዓለማየሁ፣ አቶ አስመላሽ ወልደማርያም፣ አቶ ስማቸው ከበደ (የኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ባለቤት)፣ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የአገር ውስጥ ኃላፊ የነበሩትን አቶ ወልደ ሥላሴ ወልደ ሚካኤልን ጨምሮ በድምሩ 24 ተከሳሾችን በክሱ አካቷል፡፡
አቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ በአቶ ከተማ ከበደ ላይ ቀርቦ የነበረን የአራጣ ማበደር ወንጀል ክስ በማቋረጥ፣ አቶ በላቸው ደግሞ አቶ ስማቸው ከበደ ለኢንተርኮንቴንታል ሆቴል ከቀረጥ ነፃ የ9.9 ሚሊዮን ብር ዕቃዎች ከውጭ አስገብተው ለተፈለገው ዓላማ አለማዋላቸው እየታወቀ በድጋሚ እንዲቆጠር፣ ድርጅቱ በምርመራ እንዳይጣራና በወንጀል እንዳይከሰስ ሁኔታዎችን በማመቻቸታቸው፣ የመንግሥትን ሥራ በማያመች ሁኔታ በመሥራት የሙስና ወንጀል መከሰሳቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ ይተነትናል፡፡ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩም ከአቶ መላኩና ከአቶ ገብረዋህድ ጋር በመመሳጠር ተከሰው ተመሥርቶባቸው የነበረውን ክስ እንዲቋረጥላቸው ማድረጋቸውንም ክሱ ይገልጻል፡፡ 
አቶ ገብረዋህድ ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ሃይማኖት ጋር በጋራ በቀረበባቸው ክስ፣ አቶ ገብረዋህድ ከ1978 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ በመንግሥት ሠራተኝነታቸው ከ247 ብር እስከ 5,700 ብር ይከፈላቸው ነበር፡፡ ኮሎኔል ሃይማኖት ደግሞ ከ1989 ዓ.ም. እስከ 2000 ዓ.ም. ድረስ በመከላከያ ተቀጥረው ሲሠሩ ከ790 ብር እስከ 2,145 ብር ደመወዝ ይከፈላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በተደረገ ብርበራ በተለያዩ ባንኮች የተቀመጠ ከፍተኛ ገንዘብ፣ ተሽከርካሪዎች፣ መቀሌና አዲስ አበባ ውስጥ ቤቶች፣ የተለያዩ አገሮች ገንዘቦች፣ ሰባት ሽጉጥና ሁለት ታጣፊ ክላሽ መገኘቱን ክሱ ይዘረዝራል፡፡ አቶ መርክነህ ዓለማየሁም ምርመራ እንዲቋረጥ፣ ከአቶ ባህሩ አብርሃ (ብስራት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር) 100 ሺሕ ብር ጉቦ መቀበልና ከተከሰሱበት ክስ በነፃ በማሰናበት፣ ከ1987 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ ከ2,535 ብር እስከ 10,234 ብር ያገኙ የነበረ ቢሆንም፣ ከደመወዛቸው ጋር የማይመጣጠን ከ6.5 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ አካብተው በመገኘታቸውና ሌሎችም ክሶች ተመሥርተውባቸዋል፡፡
በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የውስጥ ደኅንነት ኃላፊ የነበሩት አቶ ወልደ ሥላሴ ወልደ ሚካኤል ከግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. እስከ የካቲት ወር 2005 ዓ.ም. ድረስ ይከፈላቸው የነበረው ደመወዝ ከ1,600 እስከ 6,000 ብር ደርሶ እንደነበር ክሱ ጠቅሶ፣ ከገቢያቸው ጋር የማይመጣጠን በ175 ካሬ ሜትር ላይ ባለሦስት ፎቅ ቤት ገንብተው በ50 ሺሕ ብር ማከራየታቸውን፣ የመንግሥት ይዞታ የነበረና የሊዝ ግምቱ 2.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ 375 ካሬ ሜትር ቦታ በሕገወጥ መንገድ አጥረው ቤት የገነቡበት በመሆኑ፣ ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ ይዞ በመገኘትና ሥልጣንን ያላግባብ መጠቀም የሙስና ወንጀል መከሰሳቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ ይገልጻል፡፡ ባለሰደፍ አንድ ክላሽ፣ ስታር ሽጉጥና አንድ የጭስ ቦምብ ያለፈቃድ ይዘው በመገኘታቸው ፈቃድ የሌለው የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ እንደተመሠረተባቸውም ዓቃቤ ሕግ በክሱ አክሏል፡፡
በክስ መዝገቡ በተካተቱ 24 ተከሳሾች ላይ ዝርዝር ተደጋጋሚ ክሶች በተናጠልና በጋራ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ አቅርቧል፡፡ 
ነሐሴ 22 ቀን 2005 ዓ.ም. መሥርቻለሁ ያለውን ክስ ከ40 ቀናት ቆይታ በኋላ ጥቅምት 11 እና 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት አቅርቦ ያሰማው የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ፣ ባቀረበው ክስ ላይ ከተከሳሾች ተቃውሞ ቀርቦበታል፡፡ የተቃውሞው ምክንያትም በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ (20) ንዑስ አንቀጽ (4) መሠረት አንድ ተከሳሽ ክስ ሲመሠረትበት፣ ክሱና የማስረጃ ዝርዝር አብሮ እንዲሰጠው የተደነገገው ሕገ መንግሥታዊ መብት በኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ተሟልቶ ባለመቅረቡ ነው፡፡ በመሆኑም የተከሳሽ ጠበቆች ከፍተኛ ተቃውሞ በማቅረብ በዕለቱ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ ሌላው ያነሱት ጥያቄ የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸው ነው፡፡ ተጠርጣሪዎች በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤት የወሰነውን ትዕዛዝ በመተላለፍ የተወሰኑ ተጠርጣሪዎች ወደ ፖሊስ ማቆያ ቦታ መወሰዳቸውን በመግለጽም ጠበቆች ተቃውመዋል፡፡ 
ሌላው በራሳቸው ጠበቆች ባይሆንም በአቶ ከተማ ከበደ ጠበቃ የተነሳው ተቃውሞ፣ የአቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይ ማየት የሚችለው ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንጂ የሁለተኛ ደረጃ ፍርድ ቤት አለመሆኑን በመጥቀስ ነበር፡፡
ፍርድ ቤቱ ዓቃቤ ሕግ በጠበቆች አስተያየት ላይ ምላሽ እንዲሰጥ ሲያዘው፣ የማስረጃ ሰነድ ያላያያዘው ከቅድመ ክስ መግለጫ ጋር የሚቀርብ መስሎት በሌላ ቀጠሮ ለማቅረብ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የዋስትና መብት ጥያቄን በሚመለከት የአብዛኛዎቹ ክስ ከአሥር ዓመት በላይ የሚያሳስር አንቀጽ መጠቀሱን ጠቁሞ፣ ዋስትና እንደሚከለክል ተናግሯል፡፡ የሦስት ተከሳሾችን የዋስትና ጥያቄም እንደማይቃወም ገልጾ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ በሰጠውም ብይን ጠበቆች ያነሱት ከክሱ ጋር የሰነድ ማስረጃ መቅረብ እንደነበረበትና ሕገ መንግሥታዊ መብት መሆኑን በመጠቆም፣ እስከ ጥቅምት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. እንዲያቀርብ አዟል፡፡ ዋስትናን በሚመለከት ተጠርጣሪ ተከሳሾች አቶ ሰመረ ንጉሤ፣ አቶ ማርሸት ተስፋዬና አቶ ዳዊት መኮንን እያንዳንዳቸው 15 ሺሕ ብር አስይዘው እንዲለቀቁ አዟል፡፡ በማረሚያ ቤት ይቆዩ የተባሉ ተጠርጣሪዎችም በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ በማዘዝ ለጥቅምት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በአቶ መላኩ ፈንታ የፍርድ ቤት የሥልጣን ጉዳይ ምላሽ ሳይሰጥ ፍርድ ቤቱ አልፎታል፡፡ የዋስትና መብት የጠየቁ ተከሳሾች ቢኖሩም፣ የተጠቀሰባቸው የሕግ አንቀጽ ዋስትና እንደሚከለክል በመግለጽ አልፎታል፡፡    
በመጨረሻ ፍርድ ቤቱ ያልተያዙ ተከሳሾችን የኮሚሽኑ ሰርቪላንስ ድጋፍ ሰጭ ቡድን በቁጥጥር ሥር አውሎ እንዲያቀርባቸው አዟል፡፡ እስከ መስከረም 2006 ዓ.ም. አጋማሽ ድረስ የጊዜ ቀጠሮ ሲጠየቅባቸው የነበሩት የአቶ ስዬ አብርሃ ወንድም አቶ ምሕረት አብርሃም ላይ ግብር ባለመክፈል ወንጀልና የተሳሳተ ሰነድ በማቅረብ ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸዋል፡፡

Source, Reporter

Tuesday, October 22, 2013

ዶ/ር መረራ የፍንዳታውን ዜና “እንጠራጠረዋለን” አሉ

"በአዲስ አበባው ፍንዳታ የሞቱት ኢትዮጵያዊያን ናቸው"
bole 1
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሩዋንዳ ሰፈር የደረሰውን ፍንዳታ አስመልክቶ ኢህአዴግ ያሰራጨውን ዜና የሚቃረኑ መረጃዎችና አስተያየቶች ቀረቡ። ለኢህአዴግ ቅርበት ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች የድጋፍ አስተያየት ሲሰጡ ዶ/ር መረራ “አትፍቶ ጠፊ አጥፍቶ ይጠፋል እንጂ በሜዳ ዝም ብሎ አያጠፋም” ሲሉ ጥርጣሬ እንዳላቸው ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ትህዴን/ በፍንዳታው የሞቱት ኢትዮጵያውያን ናቸው ሲል ስም ገልጾ የኢህአዴግን ዜና አጠጥሎታል።
በፓርላማ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራ የጠየቁት ከኢህአዴግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የሚታሙ ፓርቲዎች “የጸረ ሽብርተኞች አዋጅ ሊጠናከርና ሊጠብቅ ይገባል” ሲሉ ተደምጠዋል። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ያነጋገራቸው የኢራፓ፣ የኢሴዳፓ፣ ቅንጅትና አዲአን ተወካዮች በየተራ የኢህአዴግን ዜና የሚቃወሙና በጥርጣሬ የሚመለከቱትን አውግዘዋል። በወቅቱ የቴሌቪዥን ጣቢያውም አንድነትና የሰማያዊ ፓርቲ ጠርተውት በነበረው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ “የጸረ ሽብርተኛነት አዋጅ ለሌላ ተግባር መዋሉን እንቃወማለን” በማለት የተቃውሞ ድምጻቸውን ሲያሰሙ በማሳየት ዜናውን ለማጀቢያነት ተጠቅሞበት ነበር።
በግል አስተያየታቸውን የተጠየቁት ዶ/ር መረራ ጉዲና በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው “ብዙዎች፣ እኔም ጓደኞቼም በጥርጣሬ ነው ያየነው” ሲሉ ከተቆረጠው ንግግራቸው ተደምጧል። ዶ/ር መረራ “አጥፍቶ ጠፊ አጥፍቶ ይጠፋል እንጂ በሜዳ ዝም ብሎ ራሱን አያጠፋም” ካሉ በኋላ “ስለዚህ እውነት ተደርጓል?” የሚለው ትልቁ ችግርና የጥርጣሬው መነሻ እንደሆነ አመልክተዋል።
ስለዚህ በሚል ድምዳሜ “ሰው አንዳንድ ጊዜ የኢትዮጵያ መንግስት ለራሱ ፖለቲካ ብሎ የሚያደርገው ያው የለመደው ስራ ነው” እንደሚል ዶ/ር መረራ በተቀነጨበው አስተያየታቸው ሲናገሩ ተሰምቷል። በተቃራኒ ከላይ በስም የተዘረዘሩት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ኢትዮጵያ የሽብር ጥቃት ኢላማና የአልሸባብ ስጋት ላይ ያለች አገር በመሆኗ ኢህአዴግ ህዝብን የመጠበቅና ደህንነትን የማስጠበቅ አደራ ስላለበት እነሱን ጨምሮ እንዲጠብቃቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስሙ የሚነሳውና በታጣቂ ሃይሉ ፈርጣማነት የሚታወቀው የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ  /ትህዴን/ በቦሌ ክፍለ ከተማ በቤት ውስጥ ፈነዳ በተባለው ፈንጂ ህይወታቸው እንዳለፈ የተገለጸው ሁለት የሶማሌ ዜጎች አይደሉም ሲል ከሁሉም ወገን የተሰራጨውን ዜና በዜሮ አጣፍቶታ። በፈንጂው የሞቱት ሁለት ሰዎች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ስማቸውም “ምክትል ኢንስፔክተር ሞላ መላኩ የተባሉ የፖሊስ አባልና አቶ ሞገስ አስቻለው የተባሉ ሲቪል ናቸው” ሲል የገለጸው ትህዴን የሟቾቹ ስም በመታወቂያ መረጋገጡን አመልክቷል።የመታወቂያውን ቅጂ ግን በገጹ አላተመም። ከአደጋው ጋር በተያያዘ በስፍራው ታይታችኋል በሚል በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን በመግለጽ የሶስት እስረኞችን ስም ይፋ ያደረገው ኦክቶበር 19 ቀን 2013 በራሱ ኦፊሳላዊ ድረገጽ ላይ ነው። ኢህአዴግም ቢሆን ሞቱ የተባሉትን ሰዎች ይህ ዜና እስከተጻፈበት ቀን ድረስ በሰነድ አስደግፎ አላቀረባቸውም።
በሌላ በኩል ኦክቶበር16 ለንባብ የበቃው ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 3ቀን 2006ዓ.ም. በቦሌ ክፍለ ከተማ ሩዋንዳ ማዞሪያና ቦሌ ሚካኤል መግቢያ አካባቢ በቦምብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ያለፈው ሁለት ሶማሊያውያን ሽብርተኞች መሆናቸውን ማረጋገጡን፣ የፌዴራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ማስታወቁን ዘግቧል።

SOURCE, GOLGUL FOR MORE INFORAMATION VISIT THE SITE

Monday, October 21, 2013

Current State of Political rights and Civil Liberties in Ethiopia:


In Freedom House’s 2013 Index of Freedom, Ethiopia’s rating is “NOT FREE,” the same rating it has earned in the last three years.[ix] Another part of that study was Freedom of the Net. Out of the sixty countries in the study that earned a lower score in terms of Freedom on the Net than Ethiopia were Syria, China (PRC), Cuba and Iran. This should speak for itself. A quick comparison of political and civil rights between Switzerland and Ethiopia reveals vast differences, with the higher scores being desirable:
Political rights:                                                      Switzerland          Ethiopia                     
1.       Electoral process                                                                        12                           1                                                             
2.       Political pluralism and participation                                    16                           2
3.       Functioning of government                                                      11                           4
Civil liberties:
4.       Freedom of expression and belief                                            16                           3
5.       Associational and organizational rights                              12                           0
6.       Rule of law                                                                                  14                           3
7.       Personal Autonomy and individual rights                           15                           5
In terms of their study on Freedom of the Press, Ethiopia, again considered “not free,” was near to the bottom at position 44[x] out of a total of 49 Sub-Saharan African countries and 175 out of 197 countries worldwide[xi]. The Committee to Protect Journalists reports that 79 journalists have been exiled, more than any other nation. Most notable are Eskinder Nega, Reeyot Alemu, and others who have been targeted through the use of draconian laws meant to silence the most courageous voices of freedom.  Two of these laws bear mentioning:
1.      Anti-terrorism Proclamation (2009): In 2012, Eskinder Nega, Reeyot Alemu—both nominated for the Sakharov prize in the European Parliament—as well as numbers of others were sentences to years in prison, being accused of terrorism; anyone who speaks out against the government can be charged with this crime and sentenced to years in prison.
2.      Charities and Societies Proclamation: This law restricts civil society by making it illegal for organizations receiving more than 10% of its funding from foreign sources to advocate for human rights, child’s rights, rights for the disabled, women’s rights, conflict resolution between religious groups or ethnicities and other legitimate roles carried out by such non-governmental organizations and institutions. The law has closed down the work of more than 2,600 civic organizations and in their place have risen pro-government look-alike organizations.

SSOURCE, GOLGUL WEBSITE, For detail clarification see the site 

በኦጋዴን የነዳጅ ጉድጉድ ቁፋሮ ተጀመረ


ኒው ኤጅ የተሰኘው የእንግሊዝ ኩባንያ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኦጋዴን ቤዚን፣ ኤልኩራን በተባለ ሥፍራ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ ጀመረ፡፡ ኒው ኤጅ በኦጋዴን ብሎክ ሰባት፣ ስምንትና አዲጋላ በተባለ ድሬዳዋ አቅራቢያ በሚገኙ የነዳጅ ፍለጋ ቦታዎች አፍሪካ ኦይል ከተሰኘ የካናዳ ኩባንያ ጋር በነዳጅ ፍለጋ ሥራ የተሰማራ ኩባንያ ነው፡፡
ኩባንያው ኤልኩራን በተባለ በሶማሊያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ አካባቢ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ ጀምሯል፡፡
ogaden-main
ታማኝ የዜና ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኩባንያው የመቆፈሪያ ማሽኑን ተክሎ የቁፋሮ ሥራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ሳለ የቁፋሮ ባለሙያዎች በማሽኑ ላይ የቴክኒክ ችግር በማግኘታቸው የቁፋሮ ሥራውን ሳይጀምሩ አዘግይተውታል፡፡ ባለሙያዎቹ በማሽኑ ላይ ያገኙትን የቴክኒክ ችግር አስወግደው የቁፋሮ ሥራውን ባለፈው ሳምንት መጀመራቸውን ምንጮች ተናግረዋል፡፡
የሚቆፈረው ጉድጓዱ ጥልቀት 2,800 ሜትር እንደሆነና የቁፋሮውን ሥራ ለማጠናቀቅ ሦስት ወራት ያህል እንደሚፈጅ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከሦስት ወራት በኋላ በጉድጓዱ ውስጥ ነዳጅ መኖርና አለመኖሩን የሚጠቁም የሙከራ ሥራ እንደሚሠራ ታውቋል፡፡
አፍሪካ ኦይል በቅርቡ በድረ ገጹ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ከኒው ኤጅ ጋር በመተባበር በኦጋዴን ላይ አተኩሮ እንደሚሠራ ገልጿል፡፡
አፍሪካ ኦይል በኤልኩራን የነዳጅ ክምችት እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ መገኘቱን ጠቅሶ፣ አሁን በሚቆፈረው ጉድጓድ በአካባቢው የሚገኘውን የነዳጅ ክምችት መጠን ለማወቅ እንደሚቻል አስታውቋል፡፡
‹‹በኤልኩራን ነዳጅ መኖሩ ይታወቃል፡፡ አሁን ዋናው ሥራ የሚሆነው በሚቆፈረው ጉድጉድ ውስጥ የነዳጅ ፍሰት እንዲከሰት በማድረግ በአካባቢው የሚገኘውን የነዳጅ ክምችት መጠን ማወቅ ነው፤›› ምንጮች ተናግረዋል።
ሪፖርተር ያነጋገራቸው የፔትሮሊየም ባለሙያዎች በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ቴኔኮ የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ በኤልኩራን በቆፈረው የመጀመሪያ የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ የተፈጥሮ ዘይት ፍሰት ማግኘቱን አስታውሰው፣ በወቅቱ ኩባንያው ክምችቱ በቂ አይደለም በሚል ትቶት ሄዷል ብለዋል፡፡ አክለውም አሁን ባለው ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቅመው አፍሪካ ኦይልና ኒው ኤጅ በኤልኩራን ከፍተኛ መጠን ያለው የነዳጅ ክምችት ሊያገኙ እንደሚችሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡ ዜናው የሪፖርተር ነው

SOURCE, GOLGUL WEBSITE KE EHUD ESKE EHUD